ጀግንነት የታጋይነት፣ የጽናትና የአሸናፊነት ውጤት ነው – ጠ/ሚ ዐቢይ
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)ጀግንነት የታጋይነት፣ የጽናትና የአሸናፊነት ውጤት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት ”ጀግንነት መልከ ብዙ ነው” ብለዋል፡፡
በዚህም የጦር፣ የግብርና ፣ የሳይንስ፣ የንግድ፣ የዕውቀት፣ የኪነ ጥበብ፣ የመንግሥት ሥራ፣ የአገልግሎት ሰጪ፣ ወዘተ ጀግኖች መኖራቸውን ገልጸዋል።
አንዱ ጀግንነት ያለ ሌላው አይኖርም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ ሀገር በራሷ ቆማ፣ ራሷን ችላ፣ የራሷን ዕድል እንድትወስን ሁሉም ዓይነት ጀግኖች ያስፈልጓታል ብለዋል።
አክለውም ሀገር የምትጎዳው ጀግኖች በጎደሉበት መስክ መሆኑን አንስተዋል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!