Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ ለአዲስ ዓመት የቅድመ አደጋ ዝግጁነት ስራ መሰራቱ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በመዲናዋ ለአዲስ ዓመት የቅድመ አደጋ ዝግጁነት ስራ መስራቱን አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳት እና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ።

ኮሚሽኑ የአዲስ ዓመት በዓልን ጨምሮ የመስቀል እና የኢሬቻ በዓላትን ተከትሎ ሊከሰቱ ከሚችሉ ማናቸውም ድንገተኛ አደጋዎች ማህበረሰቡን መታደግ የሚያስችለውን የቅድመ አደጋ ዝግጁነት ስራ መስራቱን አስታውቋል።

ይህ የተገለፀው የኮሚሽኑ የአደጋ ምላሽ ዘርፍ ከማዕከሉ እና ከቅርንጫፍ መስሪያ ቤቶቹ ሰራተኞች ጋር ባደረገው ውይይት ላይ ነው።

ኮሚሽኑ በበኩሉ ቅድመ ዝግጅቱን ያጠናቀቀ ቢሆንም አደጋ ሳይከሰት ቀድሞ ለመከላከል የሕብረተሰቡ ተሳትፎ ጉልህ ሚና አለው ብሏል።

በመድረኩም በ2014 ከመስከረም ወር ጀምሮ ለሚከበሩት ሶስት በዓላት ማለትም÷ በአዲስ ዓመት፣ በመስቀል እና በኢሬቻ በዓላት ለአደጋ ጊዜ የምላሽ አገልግሎት ለመስጠት የሚውሉ በቂ ግብአቶች እና ተሽከርካሪዎች መመደባቸውን ገልጿል።

በዚህም መሰረት በአስር ክፍለ ከተማ 918 የአደጋ ሠራተኞች ፣ 39 ከባድ የአደጋ ተሽከርካሪዎች እና 22 የቅድመ ሆስፒታል አገልግሎት የሚሰጡ አምቡላንሶች ዝግጁ መሆናቸው ተገልጿል።

ሆኖም ግን ጥንቃቄ እየተደረገ ለሚገጥም ማንኛውም አደጋ :-

በነፃ የስልክ መስመር 939

እንዲሁም በቀጥታ የውስጥ መስመሮች :-

0111555300

0111568601

ወይም 0111264848

ላይ በመደወል አገልግሎቱን 24 ሰዓት ማግኘት እንደሚችሉ ኮሚሽኑ አስታውቋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.