Fana: At a Speed of Life!

በቀዳማዊ እመቤት ፅ/ቤት በ800 ሚሊየን ብር የዳቦና ዱቄት ፋብሪካዎች ሊገነቡ ነው

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀዳማዊት እመቤት ፅህፈት ቤት እና ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በአስር ከተሞች ለሚሰሩ አስር የዳቦ እና የዱቄት ፋብሪካዎች ግንባታ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ፡፡

ዳቦ ቤቶቹ በአስር ከተሞች የሚገነቡ ሲሆን÷ የዳቦና የዱቄት ፋብሪካዎችን በአንድ ላይ አጣምረው የሚይዙ ይሆናል ነው የተባለው፡፡

የሚገነቡት ፋብሪካዎች እያንዳንዳቸው በቀን 400 ኩንታል ዱቄት የማምረት እና 300ሺህ ዳቦ የመጋገር አቅም እንደሚኖራቸው የተገለፀ ሲሆን÷ በአስሩም ከተሞች ሰርቶ ለማጠናቀቅ 12 ወራት እንደሚፈጅ ተገልጿል፡፡

ፕሮጀክቱ የከተሞቹን የዳቦ ፍላጎት ከማሟላት ባለፈ ለ1ሺህ 200 ሰዎች የስራ እድልን እንደሚፈጥርም ነው የታወቀው፡፡

ለአጠቃላይ ፕሮጀክቱ በጀት 800ሚሊየን ብር የተያዘለት ሲሆን÷ ፋብሪካዎቹ ሰመራ፣ ጅግጅጋ፣ ሀረር፣ ነቀምት፣ ጎንደር፣ ደሴ፣ አሶሳ፣ ሀዋሳ፣ ወላይታ ሶዶ እና ቦንጋ ይገነባሉ ነው የተባለው፡፡

በፈቲያ አብደላ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.