Fana: At a Speed of Life!

ግጭትን ለማስቆም የህብረተሰቡን የመፍትሔ ሃሳቦች ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ተጠቆመ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ግጭትን ለማስቆም ህብረተሰቡ የሚያነሳቸው የመፍትሔ ሃሳቦች ከውይይት ባለፈ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ተመለከተ።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ግጭትን መከላከልና እርቀ ሰላም ግንባታ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በአሶሳ ከተማ ተካሂዷል፡፡

የውይይቱ ተሳታፊዎች እንዳሉት÷ ግጭት በአግባቡ ካልተያዘና ካልተፈታ ከመብረድ ይልቅ እየተባባሰ የመምጣት እድሉ ሰፊ ነው፡፡

በክልሉ መተከል ዞን ለዓመታት የተከሰቱትን ግጭቶች የጠቀሱት ተሳታፊው÷ ችግሩ እንዲፈታ የተካሄዱ የእርቀ ሠላም መድረኮችን የሚመሩ ግለሰቦች ሰላምን ከማውረድ ይልቅ የግል ጥቅማቸውን እንደሚያስቀድሙ ተናግረዋል፡፡

በመተከል እርቀ ሰላም ከተካሄደባቸው ቦታዎች መካከል በአብዛኞቹ ግጭት ዳግም የተቀሰቀሰበት ሁኔታ መኖሩንም ገልጸዋል፡፡

ግጭት እንዲቆም በተደጋጋሚ ህዝባዊ የውይይት መድረኮች መካሄዳቸውን አስታውሰው÷ በመድረኮቹ በህብረተሰቡ የተነሱ የመፍትሄ ሃሳቦች ከመድረክ ፍጆታ ባለፈ ተግባራዊ መደረግ አለባቸው” ብለዋል፡፡

በግጭት አፈታት የህብረተሰቡን ባህላዊ እሴቶች በሚገባ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚያስፈልም ነው የጠቆሙት፡፡

አመራሮች በየመድረኩ ለህዝብ የሚገቡትን ቃል በቁርጠኝነት መፈጸም እንዳለባቸው መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.