Fana: At a Speed of Life!

የመቄት ወረዳ ከአሸባሪው ቡድን ነጻ ወጣች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 1፣ 2014 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን በመቄት ወረዳ ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል፡፡
የተራረፈው የቡድኑ ርዝራዥም በደብረ ዘቢጥ፣ በአግሪት፣ በፍላቂትና በገረገራ ተለቅሞ ከተሞቹ መደበኛ እንቅስቃሴ መጀመራቸው ተገልጿል፡፡
አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን አሁን ላይ በወገን ጦር በጋሸና እየደረሰበት ያለውን ከፍተኛ ድብደባ መቋቋም አቅቶት ወደ ኋላ እየፈረጠጠ መሆኑን የግንባሩ የጦር መሪዎች አስታውቀዋል፡፡
አሸባሪውና ወራሪው የትህንግ ቡድን የደረሰበትን ጥቃት መቋቋም ባለመቻሉና አካባቢው ሙሉ በሙሉ ነጻ በመውጣቱ አዲሱን ዓመት በድልና በደስታ እያሳለፉ መሆናቸውን የግንባሩ የጦር መሪዎች አሚኮ ዘግቧል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.