በመዲናዋ በፖሊስ ኮሌጅ ስልጠና የወሰዱ ወጣቶች ተመረቁ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ በፖሊስ ኮሌጅ ስልጠና የወሰዱ 259 ወጣቶች ተመረቁ።
ከተመራቂዎቹ መካከል 32ቱ የፖሊስ አባላት ሲሆኑ÷ ቀሪዎቹ የማርሻል አርት ስፖርተኞችና በጎ ፍቃደኛ የሰላም አስከባሪዎች ናቸው።
ሰልጣኞቹ ወደ ስራ ሲሰማሩ የአካባቢያቸውንና የከተማዋን ሰላም በማስጠበቅ ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸውየተገለጸ ሲሆን÷ በቀጣይም ወጣቶችን ለማሰልጠን የምልመላ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑ ተጠቅሷል።
ስልጠናው “እኔ የከተማዬ የሰላም ዘብ ነኝ” በሚል መርህ መከናወኑም ተገልጿል።
በስነ-ስርዓቱ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ የከተማዋ ከፍተኛ የመንግስት ስራ ሃላፊዎች መገኘታቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!