Fana: At a Speed of Life!

ዞኑ በወረባቦና በተሁለደሬ ወረዳዎች በትህነግ ወረራ ጉዳት ለደረሰባችው ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ወሎ ዞን ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት በወረባቦና በተሁለደሬ ወረዳዎች በሽብርተኛው ትህነግ ወረራ ጉዳት ለደረሰባችው ወገኖች ድጋፍ አደረገ።

ጽሕፈት ቤቱ 1ሺህ ኩንታል ዱቄት፣ 2 ሺህ ሊትር ዘይት፣ 4 ኩንታል የሕጻናት አልሚ ምግብ እና 1 ሺህ ብርድ ልብስ ነው ለተጎጂዎቹ ድጋፍ ያደረገው፡፡

የደቡብ ወሎ ዞን ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ መሳይ ማሩ ድጋፉ በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.