Fana: At a Speed of Life!

በህወሓት ኃይሎች በቆቦ ከተማና በዙሪያው በሚገኙ ሲቪል ሰዎች ላይ እየተፈጸመ ያለው ጥቀት በአጅጉ አሳስቦኛል – የኢትዮጵያ ሠብዓዊ መብቶች ኮሚሽን

 

በህወሓት ኃይሎች በቆቦ ከተማና በዙሪያው በሚገኙ ሲቪል ሰዎች ላይ እየተፈጸመ ያለው ጥቃት በአጅጉ አሳስቦኛል – የኢትዮጵያ ሠብዓዊ መብቶች ኮሚሽን

አዲስ አበባ መስከረም 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የህወሓት ኃይሎች በቆቦ ከተማና በዙሪያው ባሉ የገጠር ከተሞች ሲቪል ሰዎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እየፈጸሙ መሆናቸው በእጅጉ አሳስቦኛል ሲል የኢትዮጵያ ሠብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ገለጸ፡፡

ኮሚሽኑ ዛሬ ባወጣው መግለጫ በህወሓት ወረራ ስር ባሉት አካባቢዎች በሚኖሩ ሲቪል ሰዎች ላይ የቤት ለቤት አደጋና ግድያ፣ ዝርፊያ እንዲሁም በመሠረተ ልማቶች ላይ ጥቃት እተየፈጸመ መሆኑን ሪፖርት እንደደረሰው ገልጿል፡፡

ኢሰመኮ የሚያደርገውን ምርመራ እንደሚቀጥልና በግጭቱ የሚሳተፉ ወገኖች በማናቸውም ወቅት ሲቪል ሰዎችን የመጠበቅ ግዴታቸውን እንዲያከብሩም አሳስቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.