Fana: At a Speed of Life!

መከላከያ ሠራዊትን ለሚቀላቀሉ የደሴ ከተማ ወጣቶች አሸኛኘት ተደረገ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) የሃገር መከላከያ ሠራዊትን ለሚቀላቀሉ የደሴ ከተማ ወጣቶች አሸኛኘት ተደርጎላቸዋል፡፡

ወጣቶቹ “ለእናት ሃገራችን በችግሯ ጊዜ ቀድመን መስዋእት ልንሆንላት መከላከያ ሠራዊትን ለመቀላቀል ወስነናል” ብለዋል።

“መከላከያን ለመቀላቀል የወሰነው በራሳችን ፈቃድ ነው፣ የኢትዮጵያን ጠላቶች ለመመከትና ሃገራችን ተከብራ እንድትኖር ለማድረግ ተዘጋጅተናል” ማለታቸውን የዘገበው አሚኮ ነው፡፡

የደሴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አበበ ገ/መስቀል÷ ወጣቶች በራሳቸው ፈቃድ የመከላከያ ሠራዊትን ለመቀላቀል ያሳዩት ተነሳሽነት የሚደነቅ ነው ብለዋል፡፡

በደሴ ከተማ በተሰራው ስራ ጥሩ ውጤት መገኘቱን ገልጸው÷ ሌሎች ወጣቶችም የሀገር መከላከያ ሠራዊትን በመቀላቀል ለሀገር ደጀን እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.