Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያ የሰብዓዊ  እርዳታ ለማድረስ ብሪታኒያ ከመንግስት ጎን ነች-የብሪታኒያ ልዩ መልዕክተኛ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የገንዘብ ሚንስትር ዴኤታ ዶክተር ኢዮብ ተካልኝ እና ያስሚን ዎሃብረቢ ከብሪታኒያ ልዩ መልዕክተኛ ኒክ ዳየር ጋር በሰብዓዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም በኢትዮጵያ ረሃብን ለመከላከል በሚሰሩ ስራዎች እና የሰብዓዊ እርዳታ ጉዳይ ላይ መክረዋል፡፡

ልዩ መልዕክተኛው የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት የቆየ መሆኑን በመጥቀስ ብሪታኒያ በኢትዮጵያ አፋር፣ አማራ እና ትግራይ ክልሎች የሰብዓዊ እርዳታ ለማድረስ መንግስትን እንደምትደግፍ መግለጻቸውን ከገንዘብ ሚንስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
 
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.