Fana: At a Speed of Life!

ምክትል ከንቲባዋ የአዲስ አበባን ወጣቶች አመሰገኑ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ወጣቶች ለከተማችሁ ብሎም ለኢትዮጵያ ሰላምና ደህንነት እያበረከታችሁ ላለው አስተዋጽኦ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ ሲሉ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ አዳነች አበቤ ገለጹ ።

አክለውም “እኔ የከተማዬ የሰላም ዘብ ነኝ” በሚል መርህ መሰረታዊ የሰላምና የፀጥታ ስልጠና የወሰዱ 27 ሺህ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በክፍለ ከተሞች ወደ ስራ በመግባት ላይ መሆናቸውንም አስታውቀዋል።

መላው የከተማችን ነዋሪዎች በስራ ስምሪታቸው ወቅት ለእነዚህ በጎ ፈቃደኛ የሰላም ዘብ ለሆኑ ወጣቶች አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ከወዲሁ አሳስባለሁ ሲሉም በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አስፍረዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.