Fana: At a Speed of Life!

ዶ/ር አረጋና ቤተሰቦቻቸው በደሴ ከተማ ለሚገኙ ተፈናቃዮች ድጋፍ አደረጉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዶክተር አረጋ ይርዳውና ቤተሰቦቻቸው ከሰሜን ወሎ የተለያዪ አካባቢዎች ተፈናቅለው በደሴ ከተማ ለሚገኙ ወገኖች ድጋፍ አድርገዋል፡፡

ድጋፉ የምግብ እህል አልባሳት እንዲሁም የቤት ቁሳቁስን ያካተተ ሲሆን÷ በቅዳሜ ገበያ ትምህርት ቤት ለተጠለሉ ተፈናቃዮች መድረሱም ተገልጿል፡፡

ድጋፉን ያደረጉት ዶክተር አረጋ÷ ሀገር ከችግር ትወጣ ዘንድ ሁሉም በአቅሙ ሊደግፍ ይገባል ብለዋል።

የተፈናቃዮቹ ሁኔታ ልብ የሚነካ በመሆኑ÷ ሁሉም በአለው አቅም ድጋፍ ሊያደርግ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡

ዶክተር ይህ ድጋፍ የመጀመሪያ ዙር መሆኑን ጠቁመው÷ በቀጣይም ተጠነክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

በከድር መሀመድ እና በሀብታሙ ተክለስላሴ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.