አንድነት ፓርክ ከቅዳሜ እስከ ረቡዕ ድረስ ለጎብኚዎች ዝግ እንደሚሆን ተገለጸ
አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) አንድነት ፓርክ ከመጭው ጥር 30 እስከ የካቲት 4 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ ለጎብኚዎች ዝግ እንደሚሆን ተገለጸ።
በእነዚህ ቀናት ፓርኩን ለመጎብኘት ትኬት የቆረጡ ጎብኚዎች ከሀሙስ የካቲት 5 ቀን ጀምሮ ጉብኝታቸውን ማከናወን እንደሚችሉም ፓርኩ ገልጿል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ በአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ የመጡ እንግዶችን የአንድነት ፓርክን ጨምሮ በከተማዋ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን ለማስጎብኘት ዝግጅት ተጠናቋል።