Fana: At a Speed of Life!

በጣሊያን እና በግሪክ የድጋፍ ማሰባሰቢያ መርሀግብር ተካሄደ

 

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ለተፈናቀሉ ወገኖች እና ለሀገር መከላከያ ሰራዊት የድጋፍ ማሰባሰቢያ መርሀግብር ተካሄደ።

በኢትዮጵያ በጦርነት ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች እና ለመከላከያ ሰራዊት “እኔ ለሀገሬ ሀገሬም ለኔ” በሚል መሪ ቃል የሚሰበሰበው የገንዘብ ድጋፍ በጣሊያን ሮም፣ በሚላን፣ ቱሪን እና በግሪክ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

በጣሊያን ባለሙሉ ስልጣን ክብርት አምባሳደር ደሚቱ ሐምቢሳ በአሁኑ ወቅት ከምንጊዜውም በላይ ከሀገራቸው ጎን መቆም እንደሚገባና ድጋፋቸውንም አጠናክረው እንዲቀጥሉ ማሳሰባቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.