Fana: At a Speed of Life!

ዶ/ር ሊያ ታደሰ ጅግጅጋ ገቡ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 18፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ)በጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የተመራውና የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ሚኒስትር ዴኤታዎችና ሌሎች ባለሙያዎችን ያካተተው ልዑክ ዛሬ ጅግጅጋ ገብቷል።

ልዑኩ ጅግጅጋ ሲገባ የሶማሊ ክልል ምክትል ፕሬዚደንት አቶ ኢብራሂም ኡስማን፣ የሶማሊ ክልል ፕሬዝዳንት ፅህፈት ቤት ሀላፊ ዶክተር ሁሴን ሄሺና ሌሎች ከፍተኛ የክልሉ የስራ ሀላፊዎች ለልዑኩ ደማቅ አቀባበል አድርጓል።

ልዑኩ ነገ በጅግጅጋ ከተማ የሚጀመረው አመታዊው የጤና ዘርፍ የምክክር ጉባኤ ላይ እንደሚሳተፍ ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.