Fana: At a Speed of Life!

በትምህርት ዘርፉ የኮቪድ-19 ክትባትን ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በትምህርት ዘርፉ ውስጥ የኮቪድ-19 ክትባትን ተደራሽ ለማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ከሚመለካታቸው አካላት ጋር ውይይት ተካሂዷል።

የኮቪድ-19 ስርጭትን በትምህርት ዘርፉ ውስጥ ለመቀነስ ክትባቱ ለመምህራን እና በትምህርት ዘርፉ ላይ ለሚሰሩ አካላት ለማዳረስ እየተሰራ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።

በመድረኩም የኮቪድ -19 ክትባትን በትምህርት ዘርፉ በተለይ በትምህርት ቤት እና ዩኒቨርስቲዎች ተደራሽ ለማድረግ አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁም ተነግሯል።

በቀጣይ ዘመቻ በመንግስት እና በግል ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩ መምህራንን የመከተብ ስራ እንደሚሰራ ነው የተገለፀው።

በተጨማሪም በኮቪድ-19 ክትባት ላይ ያለውን የተዛባ ግንዛቤም ለማሻሻል ትምህርት ቤቶች ላይ በቀጣይነት መሰራት እንዳለበትም መገለፁን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

አካባቢዎን ይጠብቁ!

ወደ ግንባር ይዝመቱ!

መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.