የአሸባሪዎቹን ህወሓትና ሸኔን የሚያወግዝ ሰልፍ በሶዶ ከተማ እየተካሄደ ነው
አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 27፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሸባሪዎቹን የህወሓትና የሸኔን ሀገር የማፍረስ ድርጊትን የሚያወግዝ ታላቅ ህዝባዊ ሰልፍ በወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል ።
በሰልፉ በዞኑ ከሚገኙ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ሰልፈኞቹ የአሸባሪዎቹን የህወሓትንና የሸኔን ሀገር የማጥፋት የጭካኔ ድርጊቶችን በአንድነት እንመክታለን!
ኢትዮጵያ የምትሸነፍ ሀገር አይደለችም !
አከባቢዬን እጠብቃለሁ ሀገሬን ለማዳን እዘምታለዉ!
ሁላችንም በጋራ የጥፋት ሀይሎችን ልንመክታቸዉ ይገባል !
የትህነግን ተልዕኮ የሚያስፈፅሙ በየአካባቢው ተሰግስገው የሚገኙ ባንዳዎችን በማጋለጥ የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል ።
በጀግኖቻችን ደምና አጥንት የተገነባች ሀገር በአሸባሪዎቹ የህወሓትና ሸኔ እኩይ ድርጊት አትፈርስም ።
በከሀዲዎች መቃብር ላይ የኢትዮጵያን ብልጽግናን እናረጋግጣለን የሚሉና ሌሎች መፈክሮችን በማሰማት ላይ ይገኛሉ ።
በአበበች ኬሻሞና በኢብራሂም ባዲ
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!