Fana: At a Speed of Life!

የስልጤ ዞን ነዋሪዎች ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ከ10 ነጥብ 1 ሚለየን ብር ድጋፍ አደረጉ

 

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 28 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ክልል የስልጤ ዞን ነዋሪዎች ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ከ10 ነጥብ 1 ሚለየን ብር በላይ በአይነትና በጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አደረጉ።

የስልጤ ዞን ነዋሪዎች ለጀግናው የመከላከያ ሰራዊት ያላቸውን አጋርነት ለመግለፅና አሸባሪው ህወሓት ቡድንን ለማውገዝ ዞን አቀፍ ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል።

በዚሁ ወቅትም የዞኑ ነዋሪዎች ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት 248 ሰንጋ በሬዎች፤ 17 ሙክት በግና ፍየል እንዲሁም 157 ሺ 2 መቶ ብር በጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል።

የአይነት ድጋፉ በብር ሲተመን ከ10 ነጥብ 1ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚሆን መገለፁን ከክልሉ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.