የጋምቤላ ክልል የመጃንግ ብሔርሰብ ዞን በሰሜን ሸዋ ዞን ለሚገኙ ተፈናቃዮች ከ3 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጣ ድጋፍ አደረገ
አዲስ አበባ፣ ህዳር 1፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ)የጋምቤላ ክልል የማጃንግ ብሔርሰብ ዞን በሰሜን ሸዋ ዞን ለሚገኙና በጦርነት ምክንያት ከተለያዩ አካባቢዎች ለተፈናቀሉ ዜጎች ከ3 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጣ ድጋፍ በደብረብርሀን ከተማ በመገኘት አደረገ ።
የመጀንግ ብሔረሰብ ዞን አስተዳዳሪ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት ድጋፉ የመጀመሪያ አለመሆኑን ጠቁመዉ ÷ ተፈናቃዮቹ የግድ እንደሚያስፈልጋቸዉ ስላመንን በሁለት ሳምንት ዉሰጥ ከዞኑ ህዝብ መሰብሰቡን ገልፀዋል ።
ዋና አስተዳዳሪዉ አቶ አብረሐም ማይክል ÷ ከዚህ በኋላም በተከታታይ ችግሩ እስከሚፈታ ህዝቡ ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል ።
የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ታደሰ ገ/ፃዲቅ በአሁኑ ሰዓት በዞናቸዉ ከ218ሺህ በለይ በጦርነቱ ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጎች መኖራቸዉን ገልፀው ÷ የመጀንግ ዞንና ህዝብ ስላደረገዉ ድጋፍ አመስግነዋል::
በጋራ ይህንን አስቸጋሪ ጊዜ እንለፈው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል ።
በዛሬዉ እለት የተደረገዉ ድጋፍ 733 ኩንታል በቆሎና ከ3ሺህ 200 በላይ አልባሳት በአጠቃላይ ከ3 ሚሊየን ብር በላይ ድጋ መደረጉን ለማወቅ ተችሏል ።
በብስራት መንግስቱ
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!