Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ ካናዳውያን ኔትወርክ ለተፈናቃዮች የ2 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ

 

አዲስ አበባ፣ ህዳር 2፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) የኢትዮጵያ ካናዳውያን ኔትወርክ ለማህበራዊ ድጋፍ ድርጅት በአሸባሪው ህወሓት ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች የ2 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡

ድጋፉ ካናዳ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በሸዋ ሰላምና ልማት ማህበር በኩል ለወሎ ተፈናቃዮች የተገኘ መሆኑን የሸዋ ሰላምና ልማት ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ ረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቼው ተናግረዋል።

ማህበሩ ተፈናቃዮች ያሉባቸውን ችግሮች ቀድሞ በማየት ደብረ ብርሃን ከተማ በአራት ትምህርት ቤቶች ለሚገኙ ተፈናቃዮች ሩዝ፣ ብርድ ልብስ፣ የመመገቢያና ማብሰያ ቁሳቁስ ፣ ዘይትና ፍራሽ ድርጅቱ ገዝቶ ማስረከቡንም ነው የተናገሩት።

ሌሎች ድርጅቶችም በዚህ መልኩ ለተፈናቃይ ወገኖች ድጋፍ እንዲያደርጉጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ካናዳውያን ኔትወርክ ለማህበራዊ ድጋፍ ድርጅት ተወካይ አቶ ከበደ ኃይለማርያም እንደገለፁት፥ ተፈናቃዮቹ አሁን ያሉበት ሁኔታ አሳዛኝና ተጨማሪ እርዳታ የሚያስፈልግ በመሆኑ በካናዳና በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እጃቸውን እንዲዘረጉ ጠይቀዋል።

ከወሎ ኡርጌሳና መርሳ ከተሞች የመጡና በደብረ ብርሃን አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሚገኙት ተፈናቃዮች እንደገለፁት፥ የነበረባቸው ቁሳቁስ እጥረት አሁን እየተቀረፈ ቢሆንም የሚደረገው ድጋፍ በቂ አይደለም ማለታቸውን ከሰሜን ሸዋ ዞን ኮሙኒኬሽን ያገኘና መረጃ ያመላክታል፡፡

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.