Fana: At a Speed of Life!

በቡታጅራ ከተማ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቡታጅራ ከተማ አሸባሪዎቹን ህወሓትና ሸኔን የሚያወግዝና መከላከያ ሠራዊትን የሚደግፍ ህዝባዊ ሰልፍ ተካሂዷል።

ክልል አቀፍ በሆነው በዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ “አሸባሪው የህውሓት ቡድን የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጠላት ነው! የሀገራችንን ሰላም እና ደህንነት ለማስጠበቅ እስከ ግንባር እንዘምታለን!” በማለት ድምጹን አሰምቷል።

ሰልፈኞቹ ካሰሟቸው ሌሎች መፈክሮች መካከል ፥ “ሁላችንም በየተሰማራንበት መስክ የህልውና ዘመቻው አካል ነን! የሀሰት ፕሮፓጋንዳ የሚነዙብንን ሚዲያዎች እናወግዛለን! ሀገራችን ኢትዮጵያን ከውስጥና ከውጭ ጠላቶች እንታደጋለን!” የሚሉ ይገኙበታል።

በሰልፉ ሥነ ስርዓት ላይ የክልል፣ የዞን፣ የከተማ አስተዳደርና የወረዳ አስተዳደር አመራሮች ተገኝተዋል።

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.