በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 1ሺህ 179 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው ዕለት በሶስት ዙር በተከናወነ ዜጎችን ከሳዑዲ ዓረቢያ የመመለስ ሥራ 1 ሺህ 179 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡
ከተመለሱት 1 ሺህ 179 ዜጎች መካከል አንድ ሕጻን እንደሚገኝበትም ነው የተገለጸው፡፡
ለተመላሽ ዜጎችም ተገቢው ድጋፍ እና እንክብካቤ ተደርጎላቸው ወደ ማቆያ ማዕከላት መሄዳቸውን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡
እስካሁን በተከናወነ ዜጎችን የመመለስ ሥራም÷ 42 ሺህ 90 ዜጎች ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው ተገልጿል፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!