Fana: At a Speed of Life!

አሜሪካ ለታይዋን ተጨማሪ ሚሳኤሎችንና ሰው አልባ አውሮፕላን ለመሸጥ እቅድ እንዳላት ተገለጸ

አዲስ አበባ ፣ጥቅምት 4 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አሜሪካ ለታይዋን ተጨማሪ ሚሳኤሎችንና ሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) የመሸጥ እቅድ እንዳላት አንድ ሪፖርት አመላከተ።
ቻይና ግዛቴ በምትላት ታይዋን ላይ እያሳደረች ያለውን ጫና ተከትሎ አሜሪካ ተጨማሪ ዘመናዊ የጦር መሳሪያዎችን ለታይዋን ለመሸጥ ማቀዷን ከነጩ ቤተ መንግስት የሚወጡ መረጃዎች ያመላክታሉ።
በዚህም የትራምፕ አስተዳደር ኤም ኬ9 ድሮኖች እና ዘመናዊ ተወንጫፊ ሚሳኤሎችን ለታይዋን ለመሸጥ ማቀዷ ነው የተሰማው።
የሽያጩ መጠንም ወደ 5 ቢሊየን ዶላር እንደሚጠጋም ነው መረጃዎች የሚያመላክቱት።
ቻይና አሜሪካ ለታይዋን ምንም አይነት መሳሪያ እንዳትሸጥ ስታሳስብ መቆየቷ ይታወሳል።
ነገር ግን የትራምፕ አስተዳደር በቻይና ላይ ጫና ለማሳደር እየሞከረ ይገኛል።
ምንጭ፡-አልጀዚራ
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.