Fana: At a Speed of Life!

አንቶኒዮ ጉተሬዝ ከሩሲያና ዩክሬን መሪዎች ጋር ሊወያዩ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 17 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ከሩሲያና ዩክሬን መሪዎች ጋር ሊወያዩ ነው።
 
ጉተሬዝ በነገው እለት ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር እንደሚወያዩ ይጠበቃል።
 
ከዚህ ባለፈም ከሁለት ቀናት በኋላ ከዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዜለንስኪ ጋር የሚወያዩ ይሆናል።
 
በውይይታቸው ለጦርነቱ እልባት መስጠት በሚቻልበት አግባብ ላይ ይመክራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ሲ ጂ ቲ ኤን ዘግቧል።
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.