Fana: At a Speed of Life!

አሜሪካ በሰሜን ኮሪያ ላይ ማዕቀብ እንዲጣል ያቀረበችው ጥያቄ በቻይና እና ሩሲያ ታገደ

አዲስ አበባ፣ ጥር 13፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) አሜሪካ በሰሜን ኮሪያ ላይ ማዕቀብ እንዲጣል ለተባበሩት መንግስታት ያቀረበችው ጥያቄ በቻይና እና ሩሲያ መታገዱ ተገለጸ፡፡

ሰሜን ኮሪያ በተደጋጋሚ የባላስቲክ ሚሳኤሎች ማስወንጭፏን ተከትሎ በአምስት ሰሜን ኮሪያውያን ላይ ማዕቀብ እንዲጣል አሜሪካ ያቀረበችው ጥያቄ ነው በቻይና እና በሩሲያ የታገደው፡፡

ቻይና የፀጥታው ምክር ቤት በሰሜን ኮሪያ ጉዳይ ላይ ዝግ ስብሰባ ከማድረጉ በፊት በሀገሪቱ ላይ ማዕቀብ እንዲጣል ከዋሽንግተን የቀረበላትን ጥያቄ ውድቅ ያደረገች ሲሆን፥ ሩሲያም በተመሳሳይ መንግድ የአሜሪካን የማዕቀብ ጥያቄ መቃወሟ ተገልጿል፡፡

የአሜሪካ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አባል አምባሳደር ሊንዳ ቶማስ-ግሪንፊልድ የሁለቱን ሀገራት ውሳኔ አስመልክተው በሰጡት አስተያየት፥ ቻይና እና ሩሲያ ጥያቄያችንን ውድቅ ማድረጋቸው በአሜሪካ ላይ ተፅዕኖ አይኖረውም ብለዋል፡፡

ማዕቀቡ ኢላማ የተደረገው ከቻይና ጋር ግንኙነት ባላቸው የሰሜን ኮሪያ ድርጅቶች ተወካዮች ላይ መሆኑን ቲ አር ቲ ወርልድ በዘገባው አስታውቋል፡፡

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.