Fana: At a Speed of Life!

አዳማ ባሮው በጋምቢያው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 27፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አዳማ ባሮው በትንሿ ምዕራብ አፍሪካዊት አገር ጋምቢያ ባሳለፍነው ቅዳሜ በተደረገው የሁለተኛው የስልጣን ዘመን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አሸናፊ መሆናቸውን የአገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን አረጋግጧል፡፡

የኮሚሽኑ ሊቀመንበር አሊዬ ሞማር ንጃይ እሁድ እለት የመጨረሻውን ውጤት ለጋዜጠኞች ይፋ ካደረጉ በኋላ ባሮው አሸናፊ መሆናቸውን በይፋ አስታውቀዋል።

ባሮው በምርጫው 53 ከመቶ ድምጽ በማግኘት አሸናፊ መሆናቸው ነው የተገለጸው።

የእርሳቸው የቅርብ ተቀናቃኝ የሆኑት ኦሳይኑ ዳርቦ ከባሮው 28 በመቶ ያነሰ ድምጽ ማግኘታቸውም ተመላክቷል።

ዳርቦ እና ሌሎች ሁለት እጩዎች ሂደቱ የአሰራር ግድፈት አለበት በማለት ውጤቱን እንደማይቀበሉ መግለጻቸውን ቲ አር ቲ ዘግቧል፡፡

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.