Fana: At a Speed of Life!

ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) የጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲን የ12ኛ ክፍል ፈተና ቅድመ ዝግጅት ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 18፣ 2015(ኤፍ ቢ ሲ) የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና የቅድመ ዝግጅትና የተማሪዎች አቀባበል ሁኔታን ተመልክተዋል።

ሚኒስትሩ ከሶማሌ ብሔራዊ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆን ነው ፈተናውን ቅድመ ዝግጅት የተመለከቱት፡፡

ብርሃኑ (ፕ/ር) በጉብኝታቸው ፥ የዩኒቨርሲቲውን አመራሮችና ተፈታኝ ተማሪዎችን ስለቅድመ ዝግጅቱ ያነጋገሩ ሲሆን ፥ ተፈታኝ ተማሪዎቹም ተረጋግተው ፈተናቸውን እንዲወስዱ አበረታተዋል።

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሐምሌ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚሰጥ ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.