Fana: At a Speed of Life!

በፕሪሚየር ሊጉ ሲዳማ ቡና ባሕር ዳር ከተማን 2 ለ 0 አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ11ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሲዳማ ቡና ባሕር ዳር ከተማን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አሳክቷል፡፡

ቀን 12 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ የሲዳማ ቡናን ግቦች ጊት ጋትኩት እና ፍቅረየሱስ ተክለብርሃን አስቆጥረዋል፡፡

በጨዋታው የባሕርዳር ከተማው ተከላካይ ያሬድ ባዬ በፈጸመው ጥፋት በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል፡፡

በተመሳሳይ ቀን 9 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ቡና እና ሀድያ ሆሳዕና ያካሄዱት ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.