Fana: At a Speed of Life!

የአፍሪካ ቦክስ ኮንፌዴሬሽን ዋና መስሪያ ቤቱን በአዲስ አበባ ሊከፍት ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ቦክስ ኮንፌዴሬሽን ዋና መስሪያ ቤቱን በአዲስ አበባ መክፈት የሚያስችል ስምምነት ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር ተፈራርሟል፡፡

ስምምነቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ እና የአፍሪካ ቦክስ ኮንፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት  አቶ ኢያሱ ወሰን መፈራረማቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

አቶ ኢያሱ ወሰን የአፍሪካ ቦክስ ኮንፌዴሬሽን በአዲስ አበባ ባደረገው ጠቅላላ ጉባዔ የኮንፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጣቸው የሚታወስ ነው፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.