አቶ አህመድ ሽዴ ከአይ ኤም ኤፍ ኃላፊ ጋር መከሩ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ከአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ኃላፊ ክሪስታሊና ጆርጄቫ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይቱ የብሄራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ እና የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) ተገኝተዋል፡፡
በውይይታቸውም ÷ በኢትዮጵያ ስላለው የሪፎርም ፕሮግራም እና ሪፎርሙን መደገፍ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡
ክሪስታሊና ጆርጄቫ አይ ኤም ኤፍ ወደፊትም ከኢትዮጵያ ጋር መስራቱን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡