Fana: At a Speed of Life!

6ኛው ሃገራዊ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን የሰሜን ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 15 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)6ኛው ሃገራዊ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን የሰሜን ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው ተወካይ ሃላፊ ኮማንደር ብዙነህ አጎናፍር ÷ምርጫው ያለምንም የፀጥታ ችግር ተጠናቋል ብለዋል።

ይህም በቂ የቅድመ ዝግጅት ስራ በመሰራቱ ነው ብለዋል ኮማንደሩ።

በ13ቱ የምርጫ ክልሎችና 1ሺህ 128 ጣቢያዎች ላይ የተሰራጩ ቁሳቁሶች ችግር እንዳይገጥማቸው ሰርተናል ነው ያሉት።

ከምርጫው ጋር ተያይዞ ጥቃቅን ችግሮች እንደነበሩ ግን አንስተዋል።

በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ የምርጫ ቅስቀሳ ሲያደርግ የነበረ እናት ፖርቲ እጩ ፍርድቤት ቀርቦ 8ሺህ ብር መቀጣቱን ተናግረዋል።

መንዝ ቀያ ላይም አንድ የብልፅግና እጩ ተወዳዳሪ ሲቀሰቅስ በቁጥጥር ስር ውሏል ብለዋል።

ለምርጫው ሰላማዊነት ከፀጥታ ሃይሉ ባሻገር ማህበረሰቡም ትልቅ አስተዋፅኦ እንደነበረው ተናግረዋል።

በቀጣይም ሰላሙን በራሱ እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል።

በሳምራዊት የስጋት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.