Fana: At a Speed of Life!

ሁሉም የኢትዮጵያ በአዓላት የኢትዮጵያውያን ፀጋዎች ናቸው – አቶ ጃንጥራር አባይ

 

አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ አንኳን ለኢሬቻ በአል በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።

ሁሉም የኢትዮጵያ ባህላዊ በአላት የኢትዮጵያውያን ፀጋዎች ናቸው ያሉት አቶ ጃንጥራር ፀጋዎቻችንን ለሕዝባችን አንድነት ፍቅር ወንድማማችንት መጠቀማችን ይቀጥላል ብለዋል።

ኢሬቻ የንጋት የብርሃን የምስራች ማብሰሪያ በአል ነው ፤መስከረም ለኛ ለኢትዮጵያውያን ልዩ ነው በአንድ በኩል ዘመን የምንቀይርበት በሌላ በኩል ትልልቅ ሃይማኖታዊና ባህላዊ በአላትን በፍቅርና በደስታ የምናከብርበት ወር መሆኑ የተለየ ያድርገዋል።

በድጋሜ መልካም የኢሬቻ በአል ይሁንልን ብለዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.