Fana: At a Speed of Life!

በሐረሪ ክልል በአንድ ቀን 100 ሺህ የችግኝ ጉድጓድ ተቆፈረ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር በሐረሪ ክልል በአንድ ቀን 100 ሺህ የችግኝ ጉድጓድ መቆፈሩ ተገለፀ፡፡

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሚስራ አብደላ ÷በሐረሪ ክልል በ2014 አረንጓዴ አሻራ 3 ነጥብ 4 ሚሊየን ችግኞች ለመትከል እቅድ መያዙን ተናግረዋል።

ከሚተከሉት 3 ነጥብ 4 ሚሊየን ችግኞች ውስጥም 2 ነጥብ 2 ሚሊየኑ ለምግብነት የሚዉሉ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

ይህም የክልሉን የአትክልት ምርትና ምርታማነት እንደሚያሳድገው ተናግረው መላው የክልሉ ነዋሪ የችግኝ ጉድጓድ ዝግጅቱን ከወዲሁ እንዲጀምር ጠይቀዋል።

በክልሉ በዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ ለመትከል በዕቅድ ከተያዘው 3 ነጥብ 4 ሚሊየን ችግኝ ውስጥ ከ2 ሚሊየን በላይ ችግኞች ዝግጅት በአራት ችግኝ ጣቢያዎቸ ተጠናቋል።

በእዮናዳብ አንዱዓለም

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.