Fana: At a Speed of Life!

ከ1 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የተልተሌ-ዋዩ-ወንዶ-ኤርቦሬ የጠጠር መንገድ ተመረቀ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 4 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ1 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የተልተሌ-ዋዩ-ወንዶ-ኤርቦሬ የጠጠር መንገድ ተመረቀ፡፡

መንገዱ የኦሮሚያ ክልልና የደቡብ ክልልን የሚያገናኝ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የመንገዱ መገንባት ለክልሎች አብሮነት ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተናግረዋል፡፡

በመንገዱ የምረቃ ስነ ስርዓት ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ባውዲ እና የሁለቱ ክልሎች የመንግስት የስራ ሃላፊዎች መገኘታቸውን ኦቢኤን ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.