Fana: At a Speed of Life!

የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 24፣ 2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት እንዲቀጥል መወሰኑን የንግድና ኢንስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የሀገሪቱን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በተረጋጋ ሁኔታ እንዲቀጥል ለማስቻል ከታህሳስ 25 ቀን 2012 ዓ.ም እስከ ጥር 30 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ ከአውሮፕላን ነዳጅ በስተቀር የሌሎች የነዳጅ ምርቶች የመሸጫ ዋጋ አሁን በስራ ላይ ባለው የመሸጫ ዋጋ ሆኖ እንዲቀጥል መወሰኑ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ገልጿል።

የአውሮፕላን ነዳጅ ዋጋ በታህሳስ ወር ሲሸጥ ከነበረበት በሊትር 28 ነጥብ 24 በዓለም ወቅታዊ ዋጋ መሰረት ተሰልቶ በተገኘው ልዩነት 1 ብር ከ08 ሳንቲም ቀንሶ በሊትር ብር 27 ነጥብ 16 እንዲሸጥ ተወስኗል።

በዓለም ገበያ ላይ የሚኖረውን የነዳጅ ዋጋ መነሻ በማድረግ እንደ አስፈላጊነቱ ማስተካከያ ሊደረግ የሚችል መሆኑም ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.