Fana: At a Speed of Life!

የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ የዒድ አልፈጥር በዓል መልካም ምኞት መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ለ1 ሺህ 441ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል መልካም ምኞት መልዕክት አስተላለፉ።

ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ በማህበራዊ ትስስር ገጾቻቸው ላይ ባስተላፉት መልዕክት “ለመላው የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ወገኖቼ መልካም የኢድ አል ፈጥር በዓል እመኛለሁ”።

ሙስሊሙ ማህበረሰብ በታላቁ የረመዳን ጾም ያሳየውን መተሳሰብና አንድነት በማጠናከር የሚገጥሙንን ችግሮችና ፈተናዎች ሁሉ በጋራ እንደምንፈታ እምነቴ የላቀ ነው ብለዋል በመልዕክታቸው።

1 ሺህ 441ኛው ኢድ አል ፈጥር ነገ እሁድ ይከበራል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.