Fana: At a Speed of Life!

ደቡብ ኮሪያ ለኢትዮጵያ ዘመናዊ የንብ ቀፎ መቆጣጠሪያ ድጋፍ አደረገች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ኮሪያ መንግስት ዘመናዊ የንብ ቀፎ መቆጣጠሪያ ለግብርና ሚኒስቴር ድጋፍ አደረገ፡፡

ማሽኑ በንቦች ላይ ምንም አደጋ ሳያስከትል የደረሰውን ማር ብቻ ከቀፎው ለማውጣት የሚረዳ ነው ተብሏል፡፡

የማሽኑ ክብደት ቀላል ስለሆነ ከቦታ ቦታ ለማንቀሳቀስ እና ለአጠቃቀም ምቹ በመሆኑ ማንኛውም ንብ አናቢ በቀላሉ መጠቀም እንደሚያስችል ተጠቅሷል፡፡

ለሙከራ የመጡት ማሽኖች ለሆለታ ምርምር ማዕከል፣ ያዩ እና ሸካ የእናት ንብ ማራቢያና ማሰልጠኛ ማዕከላት ተልኮ በዘርፉ በተሰማሩ ባለሙያዎች በሙከራ ከተረጋገጠ በኋላ በቀጣይ ግለሰቦች፣ ባለሀብቶች እና ማህበራት ገዝተው እንዲጠቀሙ ይደረጋል ነዉ የተባለዉ፡፡

በርክክብ ስነ ስርዓቱ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ፍቅሩ ረጋሳ እና የደቡብ ኮሪያ ተወካዮች በተገኙበት ርክክብ መካሄዱን ከግብርና ሚኒስቴር ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.