Fana: At a Speed of Life!

ቻይና ምንም ዓይነት ቴክኖሎጂ ከውጪ ሳታስገባ የሰራችው አውሮፕላን በዚህ ዓመት ለሽያጭ ይቀርባል

አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና ምንም ዓይነት የግንባታ ቁስ እና ቴክኖሎጂ ከውጪ ሳታስገባ የሰራችውን ሲ 919 የተሰኘ የመንገደኞች አውሮፕላን በዚህ ዓመት ለሽያጭ እንደምታቀርብ አስታውቀች፡፡

መቀመጫውን በሻንጋይ ያደረገው የቻይና የንግድ አይሮፕላን ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ ዉ ዮንግሊያንግ ÷ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ በሲ 919 ፕሮጀክት ላይ ያደረሰውን ጉዳት መቆጣጠር መቻሉን እና የአውሮፕላን ግንባታ ሥራው እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የአሜሪካው ቦይንግ አምራች ኩባንያ እና ፈረንሣይ የሚገኘው ኤርባስ በትሪሊዮን የሚቆጠር የአሜሪካ ዶላር በዘርፉ ሲያንቀሳቅሱ እንደነበረ ሲጂቲ ኤን አስታውሷል፡፡

ይህም እስከ ፈረንጆቹ 2025 ሀገሪቷ የውጭ ምንዛሬን ለማዳን ሁሉንም ምርቶች ቻይና ውስጥ ለማምረት የነደፈችውን ስትራቴጂ ከወዲሁ ያሳካ ነው ተብሎለታል፡፡

የቻይናው ሲ 919 አውሮፕላን በፈረንጆቹ ታኅሣሥ 21 ቀን 2020 ከሁቤይ ግዛት ውሃን ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በመነሳት የሙከራ በረራውንም ማድረጉ ተመላክቷል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.