Fana: At a Speed of Life!

የፋሲካ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የፋሲካ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ እየተከበረ ይገኛል።

ፋሲካን በማስመልከት የሃይማኖት አባቶች ባስተላለፉት መልዕክት “የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓልን ስናከብር አንድነታችንን በማጠናከር እና የኢትዮጵያን ዘላቂ ሠላም ለማስፈን በተግባር በመስራት ሊሆን ይገባል” ብለዋል፡፡

“የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ የሰው ልጅ ሃጥያት የተሰረየበት ፣ ፍቅር የተገኘበት እንዲሁም እንዲሁም ደህንነት የተጎናፀፈበት ነው” ብለዋል፡፡

በዓሉን በተለያየ ምክንያት ለችግር የተጋለጡ ወገኖችን በመደገፍ እና በመንከባከብ ማሳለፍ እንደሚገባም የሃይማኖት አባቶቹ አሳስበዋል፡፡

ህዝበ ክርስቲያኑም በመላ ሀገሪቱ ሠላም እንዲሰፍን ጥረቱን እንዲያጠናክር የሃይማኖት አባቶቹ ጠይቀዋል፡፡

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.