Fana: At a Speed of Life!

በአቶ ዑመር ሁሴን የተመራ ልዑክ በደሴ ዙሪያ ወረዳ የጠባሲት ንዑስ ተፋሰስን ጎበኘ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በግብርና ሚኒስትሩ አቶ ዑመር ሁሴን የተመራ የልዑካን ቡድን በደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ዙሪያ ወረዳ የጠባሲት ንዑስ ተፋሰስን ጎብኝቷል፡፡
የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አሕመድ ጋሎ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለጹት÷ በዘንድሮ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ከ43 ሺህ ሄክታር በላይ ሽፋን ያለው የተፋሰስ ልማት መሰራቱን አስረድተዋል።
በ46 ሞዴል ተፋሰሶች ላይ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ከ285 በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
ዛሬ እተጎበኘ ያለውም የዚሁ ሥራ አካል የሆነውንና ከ2 ሄክታር በላይ ሽፋን ያለው የጠባሲት ንዑስ ተፋሰስ÷ 25 ወጣቶች ተደራጅተው አትክልትና ፍራፍሬ ለማልማት ዝግጅት እያደረጉበት እንደሚገኝም ነው ገለጹት፡፡

በጉብኝቱ ላይ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ዑመር ሁሴንን ጨምሮ በአማራ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ ወይዘሮ ዓይናለም ንጉሴ፣ የግብርና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኃይለ ማርያም ከፍያለው፣ የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አብዱ ሁሴንና ሌሎች የፌደራል፣ የክልልና የዞን አመራሮች መገኘታቸውን ከደቡብ ወሎ ዞን ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በግብርና ሚንስቴር አቶ ዑመር ሁሴን የተመራ የልዑካን ቡድን በትናንትናው ዕለት በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ  ወረዳ  በክላስተር የለሙ የማንጎ እርሻዎችና የቆላ ፍራፍሬ ችግኝ ጣቢያን ጎብኝቷል።

በ500 ሄክታር መሬት ላይ የማንጎ ክላስተር በመፍጠር አርሶ አደሮችን ወደ ፍራፍሬ ልማት ማስገባት እንደተቻለም ነው የተገለጸው።

5 ሺህ 189 አርሶ አደሮች  በወረዳው ማንጎ ክላስተር በመታቀፍ ተጠቃሚ ለመሆን በቅተዋል።

በወረዳው የፍራፍሬ ችግኝ የሚያዘጋጁ 6 ማህበራት ያሉ ሲሆን፥ የቆላ ፍራፍሬዎችን ለአጎራባች ወረዳዎችና ለአፋር ክልል ያቀርባሉ።

የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ቃልኪዳን ሽፈራው፥ ችግኞችን በበቂ ሁኔታ በማዘጋጀት በክላስተር በማደራጀትና ስልጠና በመስጠት አርሶ አደሩን ፍራፍሬ አምራች እንዲሆን እየሰራን ነው ብለዋል ።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.