Fana: At a Speed of Life!

የሶማሊያ ጦር በ39 የአልሸባብ አባላት ላይ እርምጃ ወሰደ

አዲስ አበባ፣ ጥር 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሊያ ጦር በ39 የአልሸባብ ሽብር ቡድን አባላት ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል፡፡

ጦሩ ከዓለም አቀፍ የጸጥታ አጋሮች ጋር ባካሄደው የጸረ ሽብር ዘመቻ 39 የአልሸባብ ሽብር ቡድን አባላት መገደላቸውን የሀገሪቱ ምድር ጦር አዛዥ ጄነራል ሞሃመድ ታሃሊል ተናግረዋል፡፡

የሽብር ቡድኑ አባላት በሙዱግ ግዛት ምዕራብ ሐራርዴሬ ወረዳ አካባቢ በተካሄደ የቅንጅት ዘመቻ መገደላቸውን የሶማሊያ ቴሌቪዥን ዘግቧል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.