Fana: At a Speed of Life!

አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ በጅቡቲ የሚገኙ ስደተኞችን ለመመለስ እየተሠራ ነው አሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ ከጅቡቲ መንግሥት ጋር በመተባበር በሀገሪቷ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ በቁርጠኝነት እየሠሩ መሆናቸውን ገለጹ፡፡

አምባሳደር ብርሃኑ በ “ነጋድ” የስደተኞች ማቆያ ማዕከል የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን መጎብኘታቸውን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡

በስደተኞች አያያዝ ላይ ከማዕከሉ አዛዥ ሌ/ኮሎኔል ኦማር ዩሱፍ ጋር መምከራቸውንም ነው ያመላከቱት፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.