Fana: At a Speed of Life!

ኮሚሽኑ ባለፉት አራት ወራት 64 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጉምሩክ ኮሚሽን ባለፉት አራት ወራት 64 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር በመሰብሰብ የዕቅዱን 95 በመቶ ማሳካቱን አስታወቀ፡፡

ኮሚሽኑ በአራት ወራት የተከናወኑ ሥራዎችን የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በአዳማ ከተማ አካሂዷል፡፡

በገቢ አሰባሰብ፣ ኮንትሮባንድ እና ሕገ- ወጥ ንግድን በመከላከል ረገድ የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ናቸው መባሉን የኮሚሽኑ መረጃ አመላክቷል፡፡

የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ÷ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና ዘመኑን የዋጀ እንዲሆን እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በቀጣይ ወራትም በበጀት ዓመቱ የተያዘውን የገቢ ዕቅድ ለማሳካት በሚያስችሉ ሥራዎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራ አመላክተዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.