Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያ ባሉ የንግድና ኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ ከኳታር ባለሃብቶች ጋር ውይይት ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ የንግድና ኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ ከኳታር ባለሃብቶች ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የኢትዮጵያን ወጪ ምርቶች በመቀበል እና በሀገራችን መዋዕለ-ነዋያቸውን ኢንቨስት በማድረግ ረገድ ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ ስጋቶችን እንዲሁም ስላለው ምቹ ሁኔታ ከባለሃብቶቹ ጋር ውይይት ማድረጋቸውን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴዔታ ካሳሁን ጎፌ ገልጸዋል፡፡

በቀጣይም በሁለቱ ሀገራት መካከል ስለሚኖረው ትብብር እና የንግድ ልውውጥ ዙሪያ ጠቃሚ ውይይት ማድረጋቸውንም አመላክተዋል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.