Fana: At a Speed of Life!

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል 4 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ገቢ ተሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ገቢዎች ቢሮ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ4 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡

የቢሮው ሃላፊ ወ/ሮ ህይወት አሰግድ ÷የገቢ አሰባሰቡን ውጤታማ ለማድረግ አማራጮችን የማስፋትና የህግ ማዕቀፎችን ማሻሻል ላይ ሰፊ ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል።

በዚህም ባለፉት 9 ወራት ከመደበኛና ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶች 4 አራት ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በመሰብሰብ የዕቅዱን 86 በመቶ ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል።

ገቢው ካለፉው ተመሳሳይ ወቅት አንጻር የተሻለ መሆኑን ጠቁመው÷ የባለሙያዎች ቁርጠኝነት ማሳደግ፣ በደረሰኝ አጠቃቀምና የግብር ከፋዮን ግንዛቤ የማስፋት ስራ መሠራቱን ተናግረዋል።

የገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱን በማዘመን በዘርፉ የሚስተዋለውን የገቢ ስወራ፣ ሌብነትን በመከላከል የክልሉን ገቢ አቅም ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰራም አንስተዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.