Fana: At a Speed of Life!

በ3 ሺህ ሜትር የሴቶች መሰናክል ውድድር ኢትዮጵያ የነሐስ ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ3 ሺህ ሜትር የሴቶች የመሰናክል ውድድር ኢትዮጵያ በአትሌት ሎሚ ሙለታ የነሐስ ሜዳሊያ አግኝታለች፡፡

አትሌቷ 9 ደቂቃ 26 ሰከንድ ከ63 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ነው 3ኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀችው፡፡

እንዲሁም አትሌት ሲምቦ ዓለማየሁ እና ፍሬሕይወት ገሰሰ 4ኛ እና 5ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቅቀዋል፡፡

ይህን ውድድር ኬንያዊቷ ቢያትሪስ ቼፕኮዪች 9 ደቂቃ ከ15 ሰከንድ ከ61 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ክብረወሰን በማስመዝገብ ጭምር ስታሸንፍ÷  ኡጋንዳዊቷ ፔሩዝ ቼሙታይ ሁለተኛ ሆናለች፡፡

በሰለሞን በቀለ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.