Fana: At a Speed of Life!

ተጨማሪ 300 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው 1 ሺህ 82 ሰዎች ከቫይረሱ አገግመዋል

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 6፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገው 3 ሺህ 867 የላቦራቶሪ ምርመራ 300 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።

ዶክተር ሊያ በፌስ ቡክ ገጻቸው እንደገለጹት 1 ሺህ 82 ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ አገግመዋል፡፡

እንዲሁም ባለፉት 24 ሰዓታት በቫይረሱ ምክንያት አራት ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡

እስካሁን ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች 96 ሺህ 307 ሲደርሱ 1 ሺህ 813 ሰዎች ደግሞ ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡

በአሁኑ ጊዜ ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች 19 ሺህ 420 ሲሆኑ 291 ደግሞ በጽኑ የታመሙ መሆናቸውንም ነው የገለጹት፡፡

ወረርሽኙ ኢትዮጵያ ከገባ ጀምሮ ለ1 ሚሊየን 714 ሺህ 966 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጓል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.