በሀረሪ ክልል የሀገር መከላከያ ሠራዊትን የሚደግፍ ሰልፍ ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ ሃምሌ 20፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የክልሉ ነዋሪዎች አሸባሪው ህወሓትን የሚቃወምና የሀገር መከላከያ ሰራዊትን የሚደግፍ ሰልፍ አካሂደዋል፡፡
በድጋፍ ሰልፉ ላይም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሚስራ አብደላ ፣ የክልሉ የብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ሀላፊ አቶ አብዱ ጀባር መሀመድን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ፣ የሀይማኖት አባቶች ፣ ሀገር ሽማግሌዎች እና አባገዳዎች ተገኝተዋል።
በአሁኑ ሰዓት መከላከያ ሰራዊታችን የኢትዮጵያ ጠላት የሆነው አሸባሪው ህወሓትን ለመደምሰስ ፣ የሀገራችን ሰላም በእጃችን መሆኑን ለአለም ህዝብ ለማሳየት እየከፈለ ያለውን መስዋዕትነት ለመደገፍ እና ከጎናቸው መሆናቸውን አቶ ኦርዲን ተናግረዋል፡፡
ነዋሪዎቹ ባካሄዱት ሰልፍ ላይም “እኛ የመከላከያ ደጀን ነን!” ፣ “የመከላከያ ሰራዊታችን ተከፍሎ የማያልቅ ውለታ አለብን!” ፣ “የኢትዮጵያን ክብር አሳልፎ የሚሰጥ ትውልድ የለም!” ፣ “የጦር መሣሪያ ከትግራይ ሕፃናት ትከሻ ይውረድ!” ፣ “የህወሃት ጁንታ ቡድን የኢትዮጵያ ጠላት ነው!” የሚሉ እና ሌሎች መልዕክቶችም ተላልፎበታል።
ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት የተደረገው የድጋፍ ሰልፍ የኢትዮጵያን ብሔራዊ መዝሙር በመዘርዘር የድጋፍ ሰልፉ ተጠናቋል ።
በነስሪ ዩሱፍ