Fana: At a Speed of Life!

ማንቸስተር ዩናትድ አርሴናልን 3 ለ 2 አሸነፈ

 

አዲስ አበባ፣ ህዳር 24፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) ትላንት ምሽት በተካሄደው የእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ ጨዋታ ማንቸስተር ዩናትድ አርሴናልን 3 ለ 2 አሸንፏል፡፡

የማንቸስተር ዩናይትድን የማሸነፊያ ጎሎች ቡሩኖ ፈርናንዴዝ  እና ክርስቲያኖ ሮናልዶ ሲያስቆጥሩ÷ የአርሴናልን ሁለት ጎሎች ስሚዝ ሮዉ እና ማርቲን ኦዲጋርድ አስቆጥረዋል፡፡

ማንቸስተር ዩናይትድ ማሸነፉን ተከትሎ ሶስት ደረጃዎችን በማሻሻል ሰባተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ÷አርሴናል አምስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ የነጥብ ልዩነታቸዉም ወደ ሁለት መጥበብ ችሏል፡፡

በሌላ የእንግሊዝ ፕሪሜሪሊግ ጨዋታ ቶተንሃም ሆትስፐርስ ብሬንት ፎርድን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡ ጎሎችን ካኖስ በራሱ መረብ ላይ ሲያስቆጥር ሰን ሁዊንግ ሚን ሁለተኛዉን ጎል አስቆጥሯል፡፡

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.