Fana: At a Speed of Life!

ቦርዱ ድጋሚ ምርጫ የሚካሄድባቸውን የምርጫ ክልሎችን ይፋ አደረገ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ 6ተኛው ሃገራዊ ምርጫ ድጋሚ እንዲካሄድባቸው የተወሰነባቸው የምርጫ ክልሎችን ይፋ አድርጓል፡፡

በዚህም ባስኬቶ ልዩ – ለክልል ምክር ቤት እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፣ቡሌ – ለክልል ምክር ቤት እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ጉመር 2 – የክልል ምክር ቤት መስቃና ማረቆ – ለክልል ምክር ቤት እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መሆናቸውን ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ቦርዱ በተጠቀሱት የምርጫ ክልሎች መስከረም 20 ቀን 2014 ድምጽ አሰጣጥ እንደሚከናወን ገልጿል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.